Tuesday, 4 November 2014

የሕወሓት/ኢህአዴግ መንግስት በ23 ዓመት ጉዞው ያፈራቸው ጄኔራል መኮንኖች ከወታደራዊ አመራር ሳይንስ ትምህርት እና ስልጠና አንፃር ሲመዘኑ/ በግንቦት 7 የወታደራዊ ጉዳዮች ቡድን የተዘጋጀ ጥናታዊ ፅሁፍ ክፍል 1


የሕወሓት/ኢህአዴግ መንግስት በ23 ዓመት ው ያፈራቸው

ጄኔራል መኮንኖች

 ከወታደራዊ አመራር ይንስ ትምህርት እና ስልጠና አን

ሲመዘኑ

በግንቦት  የወታደራዊ ጉዳዮች ቡድን

የተዘጋጀ ጥናታዊ ፅሁፍ

ክፍል 1

መስከረም 2007 ዓ..

ርዕስ ማውጫ

መግቢያ. 2
1…… የወታደርዊ አመራር ምንነትና ዋና ዋና የአመራር እርከኖች፤. 3
2…… የወታደራዊ አመራር የስልጠና እርከኖችና ወደ ወታደራዊ የትምህርት አካዳሚዎች መግቢያ መስፈርቶች.. 3
2.1. ወታደራዊ አካዳሚ፡ 4
2.2. ሰታፍ ኮሌጅ.. 4
2.3. የአዛዥነት እና የመምሪያ መኮንንነት አካዳሚ… 5
2.4 የጦር ኋይሎች ዋር ኮሌጅ(Armed Forces War College) 6
3…… የመኮንኖች የማዕረግ ዕድገት ሂደት.. 7
4…… የጄነራል መኮንንነት የማዕረግ ዕድገት.. 8
5…… የቀድሞው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አመራሮች የሥልጠና ሂደት፤. 10
6…… የአሁኑ  የሀገር መከላከያ መኮንኖች ከወታደራዊ አመራር ሳይንስና ጥበብ አንፃር. 11
7…… ማጠቃለያ. 13
8…… አባሪ ሰነድ- ፩ (Annex-1) 15
የሕወሓት/ኢህአዴግ መንግስት በ23 ዓመት ጉዞው  ያፈራቸው ጄኔራል መኮንኖች
ከወታደራዊ አመራር ሳይንስ ትምህርት እና ስልጠና አንፃር ሲመዘኑ

መግቢያ

 የኢትዮጵያ ሠራዊት በዘመናዊ መልክ ከተቋቋመበት ከ1927 ጀምሮ  እስክ 1983 ዓ/ም ድረስ ጊዜው በሚጠይቀው ወታደራዊ ሳይንስ የተማሩ፣  ዘመናዊ ክህሎትንና  ሥንምግባርን የተላበሱ እና  በተግባር የተፈተነ ጀግና  የምድር ጦር፣ የባህር ኃይልና የአየር ሃይል ሠራዊትና መሪዎችን  ለማፍራት የቻለ ነበር::  በሂደቱም ሰራዊቱን  ፈታኝ በሆኑ የተለያዬ አውደ ፍልሚያዎች መርተው ለድል ያበቁ ከፍተኛ ወታደራዊ ምሁራንና መኮንኖችን አፍርቶ ማለፉ የሚታወስ ነው::  የማእረግ አሰጣጡም እንዳሁኑ ዘርን መሰረት በማድረግ ሳይሆን የትምህርት ዝግጅትን፣ ወታደራዊ ዲስፕሊንና ሥነምግባርን እንዲሁም በእየእርከኑ ያሳየው ብቃትና ተገቢውን የመቆያ ጊዜ መፈፀሙ ተረጋግጦ፤ ይህንን እንዲያስፈፅም በተዋቀረ ገለልተኛ አካል አቅራቢነት በሀገሪቱ መሪዎች ሹመት ሲሰጥ ኖሯል።
 ቀደም ሲል በተገለፀው የማዕረግ እድገት አሰጣጥ ሂደት መሠረት በአጠቃላይ ከ1927 እስክ 1983 ሀገሪቱ 293 ጄኔራሎችን አፍርታ ነበር። በሌላ መልኩ ወያኔ የመንግሥት ሥልጣን ከወሰደበት ከ1983 ጀምሮ ዘርንና ታማኝነትን በቻ መሰረት በማደረግ ለ130  የቀድሞ ሽምቅ ተዋጊ መሪዎቹ ከብርጋዲየር እስከ ሙሉ ጄኔራልነት ማዕረግ አድሎአቸዋል። ከትምህርት ዝግጅት አንፃር 97 በመቶ (126ቱ) የሚሆኑት መደበኛ የወታደራዊ ሳይንስ እውቀትና ከህሎት የሌላቸው ሲሆን ቀሪዎቹ 3 በመቶ የሚሆኑት ተገቢውን የወታደራዊ ሳይንስ የተማሩና በቂ ሙያዊ ክህሎትን ያዳበሩ አራት የቀድሞ ጦር አባላት ብቻ ነበሩ (አሁን ሦስቱ በጡረታ ሲገለሉ አንዱ በፖለቲካ ጉዳይ የተባረሩ ናቸው)። በአጠቃላይ ከነዚህ 130 ጄነራሎች ውስጥ 67ቱ የሆኑ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የሕወሓት አባላት ናቸው።
የዚህ ፅሁፍ አጠቃላይ ዓላማ ባለፉት 23 ዓመታት የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ያፈራቸውን ጄኔራል መኮንኖች ከወታደራዊ ሳይንስና ሙያዊ ክህሎት አንፃር መፈተሽና መገምገም ነው። በዚህም መሰረት ይህን መግቢያ (Introduction) ጨምሮ
1ኛ፡ የወታደራዊ አመራር ምንነት እና ዋና ዋና የጦር  አመራር እርከኖች፣
2ኛ፡ የወታደራዊ አመራር የስልጠና እርከኖችና ወደ ወታደራዊ የትምህርት አካዳሚዎች የመግቢያ መስፈርቶች፣
3ኛ፡ የመኮንኖች የማዕረግ እድገት፣
4ኛ፡ የጄኔራል መኮንኖች የማዕረግ እድገት፣
5ኛ፡ የቀድሞው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አመራሮች ትምህርትና የሥልጠና ሂደት፣
6ኛ፡ አሁን ያለው የጦር ሃይል መኮንኖች የአመራር ሥልጠናና ብቃት፣
7ኛ፡ ማጠቃለያ ሲሆኑ ከዚህ እንደሚከተለው በቅደም ተከተል ይቀርባሉ።

1.    የወታደራዊ አመራር ምንነትና ዋና ዋና የአመራር እርከኖች

ወታደራዊ አመራር በተፈጥሮው የሳይንስንና የጥበብን (both Science and Art) ዘርፍ አጣምሮ የያዘና የተከበረ የሙያ መስክ ነው። ይህም በመሆኑ ማንኛውም የጦር ኃይል አባል በአመራር ቦታ ላይ ከመቀመጡ በፊት ዘመኑ የሚጠይቀውን ለየሥልጣን እርከኑ ተገቢ የሆነውን ወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ በመማርና እና ስልጠና በመውሰድ (Military Education and Training) በአጥጋቢ ሁኔታ ማጠናቀቅ ይጠበቅበታል።
የወታደራዊ አመራር (Military Leadership) ትምህርትና ሙያዊ ስልጠናውም በወታደራዊ የአመራር ንድፈ ሀሳብ ፣ ስትራቴጅና ታክቲክ ትምህርትና የተግባር  ሥልጠናን የሚያካትት ሆኖ መደራጀት ይኖርበታል።
በጦር ሀይሎች ውስጥ አመራር የሚሰጡ የአመራር አካላት በሁለት ዋና ዋና ደረጃዎች ይከፈላሉ:: እነሱም:-
1.1.   የበታች ሹም (Non Commissioned Officer/NCO)
1.2.  መኮንኖች ናቸው (Commissioned Officers) ናቸው::
የበታች ሹም (Non Commissioned Officer/NCO)፦ የሚባሉት ሰራዊቱን በቅርብ የሚቆጣጠሩ፣ የሚያደራጁ፣ የሚያሰለጥኑ፣ የሚመሩትን ሀይል ለውጊያ የሚያዘጋጁ ከፍተኛ ሀላፊነት ያለባቸው የሰራዊቱ የጀርባ አጥንት ሆነው የሚያገለግሉ መሪዎች ናቸው:: በሰራዊቱ ውስጥ በግንባር መስመር ከበላይ አካል የሚሰጣቸውን ትእዛዝ ተቀብለው በተዋረዱ የሚያዙ የሚያዋጉ እና በየትኛውም የሰራዊቱ ጠቅላይ መምሪያ ውስጥ የስታፍ ስራዎችን በኃላፊነት የሚሰሩ ናቸው:: የአመራር ብቃታቸውንም ለማጎልበትም የወታደራዊ የአመራር ስልጠናም ይወስዳሉ:: በአጠቃላይ የበታች ሹሞች በተዋጊው ሰራዊትና በአመራር መኮንኖች መካከል እንደ ድልድይ ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው::
መኮንን (Commissioned Officer/CO) ፦የሚባለው የወታደራዊ አመራር ጥበብን እና የወታደራዊ ስልት ስልጠናን ወስዶ በምድር ጦር፣ በአየር ሀይል (Pilot Officer) በባህር ኃይል (Ensign) በምክትል መቶ አለቃነት ማዕረግ የተመረቀ(ች) ወይም ከዚያ በላይ እስከ ከፍተኛ ፊልድ ማርሻል ማዕረግ የደረሰ ሁሉ መኮንን ይባላል:: ስልጠና ያልወሰደ ግን መኮንን አይባልም፡፡ አንድ መኮንን በህግ የተሰጠውን ማዕረግና ሀላፊነት ከተቀበለ በኋላ በተመደበበት የጦር ክፍል የሚመራቸውን ክፍሎች ወይም ኃይሎች  በትዕዛዝ፣ በማነቃቃት እና በማግባባት ግዳጃቸውን እንዲፈጽሙ ተጽዕኖ የማድረግ ሀላፊነት አለበት::

2.   የወታደራዊ አመራር የስልጠና እርከኖችና ወደ ወታደራዊ የትምህርት አካዳሚዎች መግቢያ መስፈርቶች

ማንኛውም የሠራዊቱ አባል መኮንን ለመሆን ከዚህ እንደሚከተለው በተዘረዘሩት መሠረታዊ  የመኮንኖች የአመራር ሳይንስና ጥበብ ሥልጠና ተቋማትና እርከኖች ውስጥ በመግባት ተገቢውን እውቀትና ክህሎት በማዳበር የሚሰጠውን የተግባርና የንድፈ ኃሳብ መመዘኛ በጥሩ ሁኔታ ማለፍና መመረቅ ይኖርበታል።የወታደራዊ አመራር የስልጠና እርከኖችም የሚከተሉት ናቸው፦
2.1.   የእጩ መኮንኖች መሰረታዊ የአመራር ስልጠና
2.2.  የስታፍ ኮሌጅ
2.3.  የአዛዥነትና የመምሪያ መኮንንነት
2.4. የጦር ኮሌጅ ናቸው::

2.1. ወታደራዊ አካዳሚ፡

ይህ አካዳሚ የዕጩ መኮንኖች ማሰልጠኛ ሲሆን ተቋሙ እንደ የሀገሩ እና አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ በጦር ኃይሎች ውስጥ እጩ መኮንኖችን መልምሎ ወታደራዊ የአመራር ጥበብና ሳይንስ በማስተማር ሠራዊቱን ለመምራት እና ለማገልገል የሚያዘጋጅና አጥጋቢ ውጤት ያመጡትን  አስመርቆ ወደ ተለያዩ የሠራዊቱ ክፍሎች እንዲሰማሩ የሚያስችል ተቋም ነው፡፡ ወደ አካዳሚው የእጩ መኮንነት ኮርስ መግባት የሚቻለው ከዚህ የሚከተሉት መስፈርቶች ተሟልተው ሲገኝ ብቻ ነው፡፡
ሀ. እድሜያቸው 17 እስክ 23 ዓመት የሆነ (የሆነች)፣
ለ. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትን በሚገባ ያጠናቀቁ ሆነው በትምህርት ቤት ቆይታቸው ወቅት ከክፍል ወደ ክፍል በሚሸጋገሩበት ጊዜ በክፍል ውጤት ደረጃቸው ከ1ኛ እስከ 5ኛ የወጡ፣
ሐ. ከፍተኛ የትምህርት ተቋም/ኮሌጅ በዲፕሎማ በጥሩ ሁኔታ የተመረቁ፣
መ. ከዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ወይም የሁለተኛ ዓመት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ፣
ሠ. ከሰራዊቱ ውስጥ ከበታች ሹማምንት ውሰጥ ፲ አለቃ እና ከዛ በላይ ሆነው በአካዳሚ እውቀታቸውና ወታደራዊ አመራር ብቃታቸው የተረጋገጠላቸው፡;
ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች አሟልተው የተመለመሉ እጩ መኮንኖችም በአካዳሚው ውስጥ ከሦስት እስከ አራት ዓመት ለሚሆን ጊዜ  የአካዳሚክ፣ የወታደራዊ ስልቶች፣ መሰረታዊ የአመራር ሳይንስና ጥበብ፣ የአካል ብቃት፣ የሞራል እና የስነ ምግባር ትምህርቶችና የተግባር ሥልጠናዎችን በመማር የብቃት መመዘኛ ፈተናዎችን በአጥጋቢ ሁኔታ ሲያሟሉ እንዲመረቁ ይደረጋሉ፡፡ የብቃት ደረጃ የሚለካባቸው መስፈርቶችም፦ የአካዳሚ ብቃት 55% ፤ የወታደራዊ ብቃት 30% እና የአካል ጥንካሬና የአትሌቲክስ ብቃት 15% ይይዛሉ፡፡ ኮርሱን ሲጨርሱና በምዘናው አጥጋቢ ውጤት ሲያመጡ በመጀመሪ ደረጃ የሳይንስ (Bachelor of Science / B.Sc) ዲግሪና በምክትል መቶ አለቃነት ማዕረግ  ይመረቃሉ፡፡ በአጠቃላይ አካዳሚው ተመራቂ መኮንኖችን በቆይታቸው ወቅት በሠራዊቱ ውስጥ የአንድ የመቶ ጦር (ኃይል) ለማዘዝ የሚያስችላቸውን  ወታደራዊ የአመራር ጥበብ ትምህርት እና የአካዳሚክስ እውቀት በሚገባ ታጥቀው እንዲወጡና በብቃት እንዲያገለግላሉ ያስችላቸዋል፡፡

2.2. ሰታፍ ኮሌጅ

ስታፍ ኮሌጅ ማለት የመካከለኛ መኮንኖች የአመራር ሳይንስና ጥበብ የሚማሩበት ተቋም ነው፡፡ በዚህ ኮሌጅ ውስጥ የሚሰጠው ትምህርት የወታደራዊ አመራር ትምህርት፣ የአስተዳደር እና የስታፍ መምሪያ መኮንንነት ተግባር እና ሀላፊነት፣ የወታደራዊ ሥነምግባር፣ የወታደራዊ ሙያ ፖሊሲ እና የአካል ብቃት ትምህርቶች ይሰጣሉ፡፡ በኮሌጁም ውስጥ በሁለት ደረጃ የተከፈሉ ሥልጠናዎች ማለትም ጁኒየር እና ሲኒየር ኮርሶች ይሰጣሉ። ወደ እዚህ ኮሌጁ ለመግባት የግድ ማሟላት የሚገባቸው መሰፈርቶች በሲኒየር የሻምበልነት ወይም በሻለቃነት ማዕረግ ሰራዊቱ ውስጥ ግዳጅን መወጣትና  ማገልገል ናቸው፡፡
ሀ. የጁኒየር ኮርስ፡ ይህ ኮርስ ሲኒየር የሆኑና የሻምበል ማዕረግ ያላቸው መኮንኖች ገብተው የሚማሩበት ፕሮግራም ነው። የሚሰጠውም የኮርስ ይዘት የወታደራዊ አመራር እና የስታፍ መኮንንነት ተግባራትን፣ የወታደራዊ ሥልቶችን እና የአካል ብቃት ሥልጠናን ያካተተ ነው፡፡ ኮርሱም የሚፈጀው ጊዜ ሃያ ሳምንት ሲሆን ኮርሱንም ሲጨርሱ የሻምበል አዛዥ ወይም በሻለቃ መምሪያ ውስጥ በስታፍ መኮንንነት የኃላፊነት ቦታ ይሰራሉ፡፡
ለ. የሲኒየር ኮርስ፡ ይህ ኮርስ ጁኒየር የሆኑ የሻለቃ ማዕረግ ያላቸው መኮንኖች የሚሳተፉበት ኮርስ ነው፡፡ ትምህርትና የሥልጠናውም ይዘት ወታደራዊ የአመራር ሳይንስና ጥበብ፣ የወታደራዊ ሥልጠናዎች፣ የአስተዳደር እና የሎጂስቲክ ትምህርቶች፣ የስታፍ መኮንንነት ተግባር እና ኋላፊነት እና የአካል ብቃት ሥልጠናዎችን ያካትታል፡፡ የኮርሱም የቆይታ ጊዜ አንድ ዓመት ነው፡፡
መኮንኖቹ ኮርሱን ሲጨርሱ የሻለቃ አዛዥ ወይም በብርጌድ መምሪያ ውስጥ የስታፍ መኮንን ሆነው ያገለግላሉ፡፡ በአጠቃላይ የስታፍ ኮሌጅ ሥልጠና የጨረሱ መኮንኖች የሚሰጣቸው የትምህርት ማስረጃ  ዲፕሎማ ነው፡፡

2.3. የአዛዥነት እና የመምሪያ መኮንንነት አካዳሚ

ይህ አካዳሚ ሲኒየር ሻለቃዎች እና ሌ/ኮሌኔሎች በመቀበል ለከፍተኛ አመራር ሰጭነት  የሚያስተምር ተቋም ነው፡፡ ወደ አካዳሚው የመግቢያ መስፈርቱም  የጁኒየር እና የሲኒየር ስታፍ ኮሌጅ ኮርሱን ካጠናቀቁ መኮንኖች ውስጥ በአመራር ስጭነታቸውና በስነምግባራቸው የሚመረጡ ይሆናል፡፡ ኮርሱም በዋነኝነት  በወታደራዊ የአመራር ጥበብ፣ ፍልስፍና፣ በወታደራዊ ታሪክ፣ በወታደራዊ ሥልቶች፣ እና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት እና የአካል ብቃት ትምህርቶች ያተኮረ ሆኖ ከ10-12 ወራት የሚሆን ጊዜን ይፈጃል፡፡ ኮርሱን አጠናቅቆ ለመጨረስ እንዲያስችላቸው  የመመረቂያ ጥናታዊ ፅሁፎችን አዘጋጀቶ ማቅረብና አጥጋቢ ውጤት ማምጣት ያስፈልጋል፡፡ መኮንኖቹም ትምህርታቸውን ሲጨርሱ በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ የማስተርስ (Master of Military Arts and Sciences) ዲግሪ ይሰጣቸዋል፡፡ ከሥልጠናው በኋላም የሥራ ኋላፊነታቸውም የሻለቃ ወይም የብርጌድ አዛዥ ወይም በክ/ጦር (በዕዝ) መምሪያ ውስጥ የመምሪያ መኮንን በመሆን ያገለግላሉ፡፡ መኮንኖቹ ከተመረቁና በያዙት ማዕረግ የተወሰነ አገልግሎት ከሰጡ በኋላ በዚሁ አካዳሚ ውስጥ እንደገና ሁለት ኮርሶችን ይወስዳሉ፡፡
እነዚህም፦
ሀ/ ከፍተኛ ወታደራዊ ጥናትና
ለ/ የዕዝ አዛዥነት
እነዚህ ኮርሶች በዋናነት የሚያተኩሩት በወታደራዊ ስትራቴትጂክ ጉዳዮች እና የዕዝ አዛዥነት ንድፈ ሀሳብ ላይ ነው፡፡ ኮርሱንም ሲጨርሱ የወታደራዊ ዕቅድ ነዳፊዎች (Strategic Military Planners) ሆነው ይመደባሉ፡፡

2.4 የጦር ኋይሎች የጦር ኮሌጅ (Armed Forces War College)

ይህ ተቋም  በወታደራዊ የሥልጠና እርከን ውስጥ የመጨረሻው የስትራቴጂክ አመራር ሥልጠና (Strategic Leadership Training) የሚሰጥበት የጥናት እና የምርምር ማዕከል ነው፡፡ በዚህ ተቋም ውስጥ የኮርሱ ተሳታፊዎች የሚሆኑት በምድር ኋይል፣ በአየር ኋይል፣ እና በባህር ኋይል ውስጥ ስትራቴጂክ አመራር (Strategic Level Leaders) እየሰጡ ከሚገኙት እና   ከከፍተኛ ስቪል የመንግስት ባለስልጣናት ውስጥ ቢያንስ ማስተርስ ዲግሪ ያላቸውን ፖሊሲና እስትራቴጂ አውጪ ሊሆኑ ይችላሉ የሚባሉትን በመቀበል ለከፍተኛ የሥልጣን ቦታ እና ሀላፊነት የሚያዘጋጅ የፖሊሲ እና የስትራቴጂ ጥናት እና ምርምር ተቋም ነው፡፡
እንደ ተለያዩ ሀገሮች ተጨባጭ ሁኔታ በጦር ሀይሎቻቸው ውስጥ እራሳቸውን የቻሉ የምድር ሀይል የጦር ኮሌጅ፣ የአየር ሀይል የጦር ኮሌጅ እና የባህር ሀይል የጦር ኮሌጅ ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ሆኖም በወታደራዊ የሥልጠና እርከን መሰረት ሁሉም ሀይሎች አመራር መኮንኖቻቸውን በየራሳቸው የጦር ኮሌጅ ትምህርታቸውን ካስጨረሱ በኋላ ወደ ዋናው የጦር ኃይሎች የጦር ኮሌጅ ገብተው እንዲሠለጥኑ ያደርጋሉ፡፡
ወደ ጦር ኋይሎች የጦር ኮሌጅ ለመግባት በቅድሚያ መሟላት ያለበት፦
  1. የአዛዥነትና የመምሪያ መኮንንነት ኮርስን መጨረስ፣
  2. በጦር ኃሎች የጦር ኮሌጅ የሚሰጠውን ኮርስ መጨረስ፣
  3. በሠራዊቱ ውስጥ በአመራር ሰጭነት ከ 22 ዓመት በላይ ማገለገል፣
  4. በወታደራዊ ሥነምግባር ምንም ችግር የሌለበትና፣
  5. የአካል ብቃቱ በሀኪም የተረጋገጠ መሆን ይኖርበታል፡;
ከላይ የተጠቀሱት መሠረታዊ መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆነው ወደ ጦር ኋይሎች የጦር ኮሌጅ የሚገቡት ለብርጋዲየር ጄኔራልነት የሚታጩ ስለሆነ በምድር ኃይል በሙሉ ኮሎኔል ማዕረግ በአየር ኋይል ተመጣጣኝ በሆነው Group Captain እና በባህር ሀይል ደግሞ ካፒቴን (Captain) በአጠቃላይ ሁሉም በኮሎኔል ማዕረግ ደረጃ ሆነው በማገልገል ያሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
የኮርሱም ተሳታፊዎች መጠንም 75 በመቶ ከጦር ኋይሎች ከሦስቱም ኃይሎች ተመጣጣኝ ቁጥር ያላቸው ከፍተኛ መኮንኖችን እና 25 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከሲቪል የመንግስት ባለስልጣናት፣ ከሀገር ውስጥ ጉዳይ፣ (በአሁኑ የፌደራል ጉዳዮች)  እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች ተመርጠው እንዲሣተፉ ይደረጋል፡፡ ኮርሱም የሚያተኩርባቸው ርዕሰ ጉዳዮችም የስታራቴጂክ አመራር ጥበብ፣ የብሔራዊ ደህንነት ስትራቴጂ ጥናት (National Security Strategy)፣ የግጭት ማስወገድ ጥናቶች (Conflic Resolution Research)፣ የህብረት ጥምር ውጊያ ፍልስፍና (War Games) እንዲሁም የጥናት እና ምርምር ንድፈ ሀሳብ ትምህርት የሚሰጥበት ማዕከል ነው፡፡ መኮንኖቹ ትምህርቱን ሲጨርሱም በስትራቴጂ ጥናት የማስተርስ ዲግሪ (Master Degree in Strategic Studies) ደረጃ  ይመረቃሉ፡፡ በጦር ኋይሎች ውስጥም የኮር ወይም የዕዝ አዛዥ ወይም በሀገር መከላከያ ጠቅላይ መምሪያ የመምሪያ መኮንነት የሥራ ኋላፊ ሆነው እንዲሠሩ ይደረጋል። በጦር ሀይሎች የጦር ኮሌጅ ውስጥ ትምህርታቸውን ጨርሰው የተመረቁ መኮንኖች ምንም አይነት የዲሲፕሊን ችግር ሪከርድ የሌለባቸው ከሆነ በቀጥታ የብርጋዴር ጄኔራልነት ማዕረግ ይሰጣቸዋል፡፡ በአጠቃላይ ከላይ የተቀመጠው  መሠረታዊ የሆነው የመኮንኖች የአመራር ጥበብ ስልጠና ሂደት ከዕጩ መኮንነት ኮርስ እስከ ጦር ኮሌጅ የሚዘልቅና መንገዱም ሌላ አቋራጭ  የሌለው ረዥም እና አስቸጋሪ ውጣ ውረድ የበዛበት መሆኑን ለማሳየት ተሞክሯል፡፡ ይህንን ረጅም መንገድ ያለፉ መኮንኖች ሁሉ የተሰጣቸውን ግዳጅ በብቃት የተወጡ ስለመሆናቸው ያለፉት ታላላቅ አውደ ውጊያዎች(በምስራቅና በሰሜን ኢተዮጵያ) ምስክርና ማስረጃዎች ናቸው፡፡

3.    የመኮንኖች የማዕረግ ዕድገት ሂደት

የመኮንኖች የማዕረግ ዕድገት መነሻውም ሆነ መድረሻው ወታደራዊ ትምህርትና ሥልጠና ነው፡፡ የወታደራዊ አመራር ሳይንስ ጥበብ ደግሞ ለመኮንነት ማዕረግና ዕድገት የማዕዘን መሰረተ ድንጋይ ሲሆን በአጠቃላይ የመኮንነት የማዕረግ  ዕድገት በሥልጠና እየታገዘ የሚከናወን ቀጣይነት ያለው ሂደት  ነው፡፡ መኮንን ለመሆን በቅድሚያ የዕጩ መኮንንነት ኮርስ ወስዶ በሚገባ ማጠናቀቅን ይጠይቃል። የአንድ መኮንን የመጀመሪያው ማዕረግም በምድር ሀይል ምክትል መቶ አለቃ (Second Lieutenant) በአየር ሀይል ፓይለት መኮንን (Pilot Officer) በባህር ሀይል ደግሞ ኢንሳይን (EnSign ) ይባላል፡፡ ምክትል መቶ አለቃ ሆኖ የተመረቀ መኮንን ወደ ሚቀጥለው የማዕረግ ዕድገት ለማለፍ የግል ሪፖርቱ ተገምግሞ ምንም ዓይነት የዲሲፕሊን ችግር ከሌለበት በምድር ሀይል ሙሉ መቶ አለቃ (Lieutenant) በአየር ሀይል በራሪ መኮንን (Flying Officer) በባህር ሀይል ምክትል ሊዩተናንት (Sub – Lieutenant) ይሆናል ፡፡ በሙሉ መቶ አለቃ ማዕረግ ደግሞ አምስት ዓመት ካገለገለ በኋላ የሻምበልነት ማዕረግ ያገኛል፤ በሻምበል ማዕረግ ደግሞ አራት ዓመት ማገልገል አለበት፡፡ በአራት ዓመት የቆይታ ወቅትም የስታፍ ኮሌጅ ኮርሱን ካጠናቀቀና በቆይታ ጊዜ ውስጥ ያስመዘገበው የወታደራዊ ዲሲፕሊን እና የሙያ ብቃቱ ተረጋግጦ በበቂ ሁኔታ ከአለፈ የሻለቃነት ማዕረግ ዕድገት ይሰጠዋል፡፡
 በሻለቃ ማዕረግ የቆይታ ጊዜ አራት ዓመት ሲሆን  በአራት ዓመት ውስጥም የአዛዥነትና የመምሪያ መኮንንነት ኮርስ ይወስዳል፡፡ የሻለቃ የማዕረግ ቆይታውን ሲጨርስ በሠራዊቱ ሕገ ደንብ መሰረት በዋንኛነት የወታደራዊ ዲሲፕሊኑ፣ የአመራር ብቃቱ፣ በተዋረድ የወሰደው የወታደራዊ አመራር ስልጠና እና በቆይታው ጊዜ ባስመዘገበው ሪፖርት ተመስርቶ ይገመገምና ወደ ሚቀጥለው የማዕረግ ዕድገት የሚያልፍ ከሆነ የሌ/ኮሎኔል ማዕረግ ይሰጠዋል፡፡ የሌ/ኮሎኔል ማዕረግ ቆይታ አራት ዓመት ሲሆን በአራት ዓመት ቆይታው ወቅት የሚወስዳቸው ኮርሶች የአዛዥነትና የመምሪያ መኮንንነት ኮርስ እንዲሁም የምድር ኃይል ወይም የአየር ኃይል የጦር ኮሌጅ የአመራር ጥበብ ሥልጠናን ወስዶ ከጨረሰና በቆይታ ጊዜውም ውስጥ ምንም ዓይነት የዲሲፕሊን ችግር ከሌለበት የሙሉ ኮሎኔልነት ማዕረግ እንዲያገኝ ይደረጋል፡፡
 ከሙሉ ኮሎኔልነት ማዕረግ ወደ ቀጣዩ ማዕረግ ለማደግ ቢያንስ የአራት ዓመት የቆይታ ጊዜ ያስፈልጋል ፡፡ በአራት ዓመት የቆይታ ጊዜ ውስጥም የጦር ኃይሎች የጦር ኮሌጅ በመግባት የስትራቴጂክ የአመራር ጥበብ መውሰደና መመረቅ ይኖርበታል:: ኮርሱንም ከጨረሰ በኋላ በቀጥታ የወሰደው የአመራር ሥልጠና እርከን፣ የአመራር ብቃቱ እና አጠቃላይ የ22 ዓመት የአገልግሎት የቆይታ ሪፖርት ተገምግሞ ከአለፈ የብ/ጄነራልነት የማዕረግ ዕድገት ይሰጠዋል፡፡ ትክክለኛ የመኮንኖች የማዕረግ እድገት አሰጣጥ ሂደትና ይዘት ከላይ በተጠቀሰው የትምህርት፣ የስልጠና፣ የሥነምግባር አፈፃፀም ግምገማ  ውጤትን መሠረት ባደረገ መንገድ የሚከናወነው ብቻ ነው፡፡

4.    የጄነራል መኮንንነት የማዕረግ ዕድገት

የጄነራል የመኮንነት የማዕረግ ዕድገት መሰረታዊ የትምህርትና ሥልጠና ዝግጁነቶች እንደተጠበቁ ሆኖ በየሀገሩ ተጨባጭ ሁኔታ  መሰረት  ይሰጣል፡፡ ለምሳሌ ያህል በአሜሪካ የጦር ኋይሎች ውስጥ የጄነራልነት ሹመት በፕሬዘዳንቱ አቅራቢነት በህግ መወሰኛው ምክር ቤት ይጸድቃል፡፡ በሌሎች ሀገሮች ግን የጄነራልነት ሹመት የሚካሄደው በመከላከያ ሚኒስቴር በሚቋቋመው የማዕረግ ዕድገት ቦርድ ወይም በመከላከያ ካውንስል በተቋቋመው በሰራዊቱ ህገ ደንብ መሠረት መመዘኛውን ያሟሉ ተመርጠው ለሀገሪቷ ፕሬዘዳንት ቀርቦ ይጸድቃል፡፡
 የጄነራል መኮንንነት ማዕረግ ከፍተኛው የወታደራዊ ማዕረግ እርከን ሲሆን በጦር ኋይሎች ( በምድር ኃይል፣ በአየር ኃይል እና በባህር ኃይል) ከፍተኛውን ኃይል የሚመሩ ወይም የሚያዙ፣ ሠራዊቱን የሚያደራጁ፣ የሠራዊቱን ህግ ደንብ የሚያወጡ፣ ሠራዊቱ የሚዋጋበትን የጦርነት ህግ እና ሠራዊቱ የሚሰለጥንበትን የሥልጠና ፖሊሲ፣ የወታደራዊ ዶክትሪን እና ስትራቴጂ የሚቀርጹ፤ በአካዳሚም ሆነ በወታደራዊ ሳይንስ እና ጥበብ የተካኑ ከፍተኛ ኃላፊነት ያለባቸው የጦር ኃየሎች ጄነራል መኮንኖች ናቸው፡፡
ሰንጠረዥ-ሀ፦ የጄነራል መኮንኖች የማዕረ አጠራር በተለያዩ የጦር ኃይል ክፍሎች
ተ.ቁ
በምድረ ኃይል
በአየር ኃይል
በባህር ኃይል
1
Brigadier GeneralAir CommodoreCommodore
2
Major GeneralAir Vice MarshalRear Admiral
3
Lieutenant GeneralAir MarshalVice Admiral
4
Full GeneralAir Chief MarshalAdmiral
5
Marshal or Field MarshalMarshal Air ForcesAdmiral of the fleet

ሀ. ብርጋዴር ጄነራል፡ ይህ ማዕረግ ከሙሉ ኮሎኔል ቀጥሎ የሚሰጥ ሲሆን የጄነራል መኮንኖች የመጀመሪያ ማዕረግ ነው፡፡ ከሙሉ ኮሎኔልነት ወደ ብርጋዴር ጄነራልነት ለመሸጋገር መመዘኛዎቹ፡
1)    በኮሎኔልነት ማዕረግ የአገልግሎት ዘመን፣
2)   የወታደራዊ የአመራር ጥበብ በተዋረድ የወሰደ፣
3)   በአገልግሎት ዘመኑ ያሳየው ዲሲፕሊን፣
4)   የወታደራዊ አመራር ብቃቱ እና ልምዱ፣
5)   በብ/ጄነራልነት ማዕረግ ሊሰራበት የሚችልበት የሥራ ቦታ ክፍት ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡
ብርጋዲር ጄነራል ማዕረግ ያለው መኮንን በጦር ኃይሎች የብርጌድ ወይም የክፍለ ጦሩ አዛዥ እንዲሁም የኮር እስታፍ ይሆናል፡፡ በያዘው ማዕረግም ከሁለት እስከ አራት ዓመት ያገለግላል፤ የጡረታ ጊዜውም በያዘው ማዕረግ አምስት ዓመት ከቆየና 30 ዓመት የአገልግሎት ዘመን ከሞላው ጡረታ ይወጣል፡፡ የጡረታ የዕድሜ ጣራውም 62 ዓመት ይሆናል፡፡
ለ.ሜጀር ጄነራል ይህ ማዕረግ ከብ/ጀኔራል ማዕረግ ቀጥሎ ያለ ባለ ሁለት ኮከብ ማዕረግ ነው፡፡ ከብ/ጀ ወደ ሜ/ጀኔራል የማዕረግ ዕድገት ለመሸጋገር በቅድሚያ ፡-
  • ክፍት የስራቦታ መኖሩ (Number of Open Positions) ፣
  • በአመራር ብቃት የፈጸማቸው ግዳጆች፣
  • በወታደራዊ ሥነ ምግባር ምንም ችግር የሌለበት፣
  • የአመራር የሥልጠና እርከን በተዋረድ የወሰደ፣
  • የአገልግሎት የቆይታ ጊዜውን (Years of Services) የጨረሰ መሆኑ መታየት ይኖርበታል።
መኮንኑ ሜ/ጀኔራል ከሆነ በኋላ የሥራ ኃላፊነቱም የክፍለ ጦር ወይም የዕዝ አዛዥ ወይም በጦር ኃይሎች ጠቅላይ መምሪያ ውስጥ የመምሪያ መኮንን ሆኖ መሥራት ነው፡፡ በያዘው ማዕረግም እስከ አምስት ዓመት ከአገለገለ በኋላ ወይም 35 ዓመት በጦር ኃይሎች ውስጥ አገልግሎት ከሰጠ ጡረታ ይወጣል፡፡ የጡረታ ዕድሜውም 62 ዓመት ነው፡፡ ከዕድሜው ጣራ ውጭ በተለየ ሁኔታ በሥራ አስፈላጊነት አራት ዓመት በተጨማሪ የመስራት አማራጭ አለው፡፡ እድሜውም እስከ 64 ዓመት ሊዘልቅ ይችላል፡፡
 ሐ. ሊዩተናንት ጄኔራል፡ ይህ ማዕረግ በሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ባለ ሦስት ኮከብ ከፍተኛ የጀኔራልነት ማዕረግ እርከን ነው፡፡ አንድ መኮንን ወደ ሌ/ጀኔራልነት ማዕረግ ከመድረሱ በፊት በጦር ኃይሎች ውስጥ በአመራር ከ 20 ዓመት ያልበለጠ አገልግሎት መስጠት አለበት፤ ከሜ/ ጀኔራል ማዕረግ ወደ ሌ/ጄነራል ማዕረግ ለመሸጋገር መሟላት ያለበት የአመራር ብቃቱ፣ በያዘው ማዕረግ የቆይታው ጊዜ፣ በወታደራዊ ሥነ-ምግባር ምንም አይነት ችግር የሌለበት፣ የአመራር የሥልጠና እርከኖችን ያለፈ፣ እና ክፍት የሥራ ቦታ መኖሩ ናቸው፡፡ ሌ/ጀኔራል ከሆነ በኋላ የሥራ ኃላፊነቱም የኮር ወይም የግንባር ወይም የህብረት የጥምር ጦር አዛዥ እና በሀገር መከላከያ ጠቅላይ መምሪያ፣ የመምሪያ መኮንን ሆኖ ማገልገል ነው፡፡ መኮንኑ በያዘው ማዕረግ ቢያንስ ሦስት ዓመት ማገልገል አለበት ነገር ግን በያዘው ማዕረግ አምስት ዓመት ከአገለገለ እና በጦር ሀይሎች ውስጥም 40 ዓመት ካገለገለ በጡረታ ይገለላል፤ የዕድሜ ጣሪያውም 62 ዓመት ይሆናል፡፡

መ. ጄኔራል፡ ይህ ማዕረግ ከሌ/ጄነራል ቀጥሎ ከፊልድ ማርሻል  ዝቅ ያለ ባለ አራት ኮከብ ማዕረግ ሲሆን በጦር ኃይሎች ማዕረግ አሰጣጥም ከፍተኛው የሹመት እርከን ነው፡፡ ከሌ/ጀኔራልነት ወደ ሙሉ ጀኔራልነት የማዕረግ እድገት ለመሸጋገር በቅድሚያ ክፍት የስራ ቦታ ሲኖር፣ በጦር ሀይሎች ውስጥም 20-23 ዓመት ያገለገለ፣ የአመራር ብቃት እና ልምዱ ስኬታማ የሆነ፣ በወታደራዊ ሥነ ምግባሩም ምንም ዓይነት እንከን የሌለበት፣ ለአመራርነት የሚሰጠውን ከፍተኛ የሳይንስና የጥበብ ሥልጠና እርከኖችን በተዋረድ የጨረሰ መሆን ይኖርበታል፡፡ የሙሉ ጀኔራል የኋላፊነት ቦታም በጦር ኃይሎች ውስጥ የምድር ጦር ወይም የአየር ኃይል አዛዥ ወይም የህብረት ዕዝ አዛዥ ወይም የጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹም ወይም የጦር ኃይሎች አዛዥ ሆኖ መሥራትን ያጠቃልላል፡፡ በያዘው ማዕረግ ቢያንስ አምስት ዓመት ያገለገለ ሆኖ በጦር ሀይሎች ውስጥ ያበረከተው የአገልግሎት ጣራ  40 ዓመት ከሞላ ጡረታ ይወጣል፡፡ የዕድሜ ጣሪያውም 64 ዓመት ይሆናል፡፡
የአንድ ሀገር የጦር ኃይል (የምድርኃይል፣ የአየር ኃይል፣ የባህር ኃይል) ከዚህ በታች በተጠቀሱት  ሦስት አይነት የአመራር ደረጃዎች  ማለትም፦
  1. በቀጥተኛ የግንባር መስመር አመራር መኮንኖች
  2. በከፍተኛ አመራር መኮንኖችና
  3. በስትራቴጂክ አመራር መኮንኖች የተደራጀ መሆን ይኖርበታል፡፡
በሰራዊቱ ውስጥ ጄነራል መኮንኖች የሆኑ ሁሉ የሥትራቴጂክ አመራር አካል ናቸው፡፡ አንድ መኮንን የብ/ጄነራል ማዕረግ ለመድረስ 22 ዓመት ማገልገል አለበት ከዚህ ውስጥ ከ7-8 ዓመታት ያለው ጊዜ የወታደራዊ የአመራር ጥበብ ሳይንስ የሚቀስምበት የዕውቀት ጉዞ መንገድ ነው፡፡
በአጠቃላይ የጄነራል መኮንኖች የወታደራዊ አመራር ጥበብ ሥልጠና መነሻው መሰረታዊ ከሆነው ከዕጩ መኮንንነት የሥልጠና እርከን ተነስቶ እስከ መጨረሻው የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ትንተና ጥናት እና ምርምር ተቋም እስከ ሆነው የጦር ኮሌጅ ድረስ ይዘልቃል፡፡ የአመራር የሥልጠና እርከኖችን ያላለፈ ጄኔራል የተሟላ ተክለ ሰውነት እንደሌለው ይታሰባል ወይም ይቆጠራል፡፡

5.    የቀድሞው የሀገር መከላከያ ሠራዊት አመራሮች የሥልጠና ሂደት፤

በሀገራችን የመከላከያ ሠራዊት ታሪክ ውስጥ የወታደራዊ ትምህርትና ሥልጠና ከፍተኛ ቦታ እና ትኩረት ነበረው፡፡ በቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት የነበረው የመከላለከያ ሚኒስቴር ሁለት የጦር አካዳሚ ትምህርት ቤቶች ነበሩት፡፡ እነዚህም የሐረር ጦር አካዳሚና የሆለታ ገነት ጦር ትምህርት ቤቶች ናቸው፡፡ የሆለታ ገነት ጦር ትምህርት ቤት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በትንሽ ዓመት ቆይታ የተቋቋመ በርካታ ብርቅዬ የጦር መኮንኖችን በጥራት ያስመረቀ ተቋም ነው፡፡ ትምህርት ቤቱ ከ1ኛ ኮርሰ እስከ 54ኛ ኮርስ ድረስ መኮንኖችን ያስመረቀ ቢሆንም በደርግ ጊዜ በነበረው የርስ በርስ ጦርነት ምክንያት የማሰልጠን ሥራውን ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ማካሄድ ተስኖት ነበር፡፡
 የሐረር ጦር አካዳሚ እ.ኤ.አ 1957 ከተቋቋመ አንስቶ እስከ ተዘጋበት 1977 ድረስ በርካታ መኮንኖችን አስመርቋል። አካዳሚው ለጎረቤት ሀገሮች ጭምር መኮንኖችን ያሰለጥን ነበር፤ ሁለቱም የጦር ትምህርት ቤቶች አለም ዓቀፍ የአመራር ስልጠና መመዘኛ ስታንዳርድን በጠበቀ መልኩ ተደራጅተው ብዙ አመራሮችን አሰልጥነው በማስመረቅ ለሃገሪቱ አበርክተዋል፡፡ ከእነዚህ የጦር አካዳሚ ት/ቤቶች ከተመረቁ መኮንኖች ውስጥ ከምክትል መቶ አለቃነት  እስከ ሌ/ጀኔራልነት ማዕረግ የደረሱ ይገኙበታል፡፡እነዚህ ጄኔራል መኮንኖች በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ የተካኑና በሥነምግባር የታነፁ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የተማሩ ከፍተኛ ብቃት እና ችሎታ ያላቸው ሀገራቸውን በወታደራዊ መስክ ያስጠሩ ብርቅዬ የኢትዮጵያ የሀገር መመኪያ ልጆች ነበሩ፡፡ የሐረር ጦር አካዳሚ  ከ1ኛ ኮርስ እስከ 21ኛ ኮርስ ድረስ በማስተማር አስመርቋል፡፡
በወቅቱ የነበሩት የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ጦር ኃይሎች የመከላከያ ሥልጠና ፖሊሲ በሚያዘው መሠረት ወታደራዊ የአመራር ጥበብና ሳይንስ በተገቢው ሁኔታ ከዕጩ መኮንን ሥልጠና እስከ ስታፍ ኮሌጅ ድረስ የዘለቁ 293 ጄነራል መኮንኖች ነበሩት(ሰንጠረዥ-ለን ይመልከቱ)።
ሰንጠረዥ–ለ፦ በሦስቱም መንግሥታት የተሾሙ ጄነራል መኮንኖች (1927–2007 ዓ/ም)
.
የማ ደረጃ
1927 እስከ 1983
ከ1983 ጀምሮ
ጠቅላላ ድምር
 ኃይለ ሥላሴ
ርግ
ህወሓት/ ኢህአዴግ
1
ጄኔራል
0
0
1
1
2
ሌ/ጄኔራል
15
3
6
24
3
ሜ/ጄኔራል
6
32
24
62
4
ብ/ጄኔራል
63
174
99
336
ጠቅላላ ድምር
84
209
130
423
በአጠቃላይ እነዚህ ጄኔራል መኮንኖች በዚህ ጽሁፍ ዋና አካል ላይ የተቀመጡትን የወታደራዊ አመራር ሥልጠና እርከኖች ይዘት እና ሂደት አሟልተው የተመረቁና በተግባር በጦር ሜዳ ውሎአቸውም አመርቂ ውጤት ያስመዘገቡ እንደነበሩ ድርሳናቸው ያስረዳል፡፡

6.    የአሁኑ  የሀገር መከላከያ መኮንኖች ከወታደራዊ አመራር ሳይንስና ጥበብ አንፃር

የዛሬው የሕወሓት ሰራዊት ከሽምቅ ተዋጊነት በቀጥታ መደበኛ የሀገሪቱ ሠራዊት እንዲሆን በምድር ሀይልና በአየር ሀይል ተከፋፍሎ  እንዲደራጀ የተደረገ ሲሆን ሠራዊቱን እንዲመሩ የተመደቡት የበታች ሹሞችና መኮንኖች በሙሉ በምንም ዓይነት ወታደራዊ የአመራር ስልጠና ውስጥ ሳያልፉና ከወታደራዊ ሙያ ሳይንስና  ሕግጋት ውጭ በዘርና በፖለቲካ ወገንተኝነት ላይ በመመሥረት ማዕረግ በጅምላ የተሰጣቸው ናቸው:: ይህ ደግሞ በሀገሪቷ መጥፎ የታሪክ ጠባሳ እየጣለ ይገኛል።
 በወታደራዊ የአመራር ስልጠና ታሪክ ያለምንም የአመራር ስልጠና የጄነራል መኮንነት ማዕረግ የሰጠች የመጀመሪያ አፍሪካዊት አገር ኢትዮጵያ ነች:: ሕወሓት/ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ከ1983 ጀምሮ እስከ 2006 ዓ.ም. ድረስ ለ130 አባሎቹ (ለዝርዘሩ አባሪ ፩ን ይመልከቱ)  የጄኔራል መኮንነት ማዕረግ የሰጠ ሲሆን 97 በመቶ የሚሆኑት ተሿሚዎችም በምንም ዓይነት የወታደራዊ አመራር ሳይንስና ጥበብ ስልጠና ውስጥ ያላለፉ ናቸው። ወደ 52 በመቶ (67ቱ) የጄኔራል መኮንንነት ቦታም የትግራይ ተወላጅ የሆኑ የህወሓት አባላት ተቆጣጥረውታል (ሰንጠረዥ-ሐን እና ሥዕል-አንድን ይመልከቱ)::
በአጠቃላይ ከላይ በሥዕሉና በሠንጠረዡ እንደተመለከትነው፤ ሂደቱ የሀገሪቱን የወታደራዊ ስልጠና ገጽታን ከማበላሸቱም በላይ መጥፎ የታሪክ ጠባሳ እየጣለ ይገኛል:: በሚገርም ሁኔታ የሀገር መከላከያ የስትራቴጂክ አመራር እንዲሰጡ በህዋሓት የተሾሙ ጄነራል መኮንኖች  መሰረታዊ የሆነውን የአመራር ስልጠና እንኳን ያልወሰዱ እና የአካዳሚክስ እውቀታቸው በጣም ዝቅተኛና በአብዛኛው ከ5ኛና ከ9ኛ ክፍል ያላለፈ መሆኑን የግል ሕይወት ታሪካቸው ያሳያል።
 አንድን ሠራዊት ለመምራትም ሆነ ለማሰልጠን ቀድሞ ሰልጥኖ መገኝት ጥያቄ ውስጥ ሊገባና ሊጣስ የማይችል መርህ ነው:: የህወሓት መንግስት ከፈጸመው አስከፊ ወንጀል አንዱ ምንም ዓይነት የወታደራዊ አመራር ትምህርትና ስልጠና ሳያገኙ ጄነራል ብሎ በመሰዬም ሠራዊት እንዲመሩ ማድረጉ ነው:: የአሁኑ ጄኔራል መኮንኖች በአካዳሚክስም ሆነ በወታደራዊ ሳይንስና የአመራር ጥበብ ድህነት የተጎዱ፣ ጫካ በነበሩበት ወቅት መደበኛ ባልሆነ የሽምቅ ውጊያ ዕውቀት ብቻ ተኮፍሰው የኖሩ አሁንም በዚያው መንገድ የሚጓዙ ናቸው::
የህወሓት ጄነራል መኮንኖች  ስለወታደራዊ አመራር ጥበብ ስልጠና ምንነትና ይዘት እንዲሁም  ሂደት  ምን እንደሆነ ግንዛቤ የሌላቸውና የማወቅ ፍላጎት የሌላቸው ናቸው፡፡ በአንድ ወቅት በአስተርጓሚ እንዲማሩ ተሞክሮ ነገር ግን ሳይሳካ መቅረቱ በተጨባጭ የሚታወቅ ነው፡፡ ምክንያቱም “አሁን እኛ ጄነራል መኮንኖች ስለሆንን አንማርም ምን ያደርግልናል” በሚል ነበር።  በአሁኑ ወቅት ሠራዊቱ እየተመራ ያለው በእነዚህ ዓይነት ሰዎች ነው! የሚገያስርመው ነገር በሚመሩት ሰራዊት ወስጥ የሚገኙ የመካከለኛ እና የዝቅተኛ አመራር መኮንኖች በወታደራዊ የአመራር ስልጠና ንድፈ ሀሳብም (Theory) ሆነ ተግባራዊ ስራዎች አለቆቻቸውን በከፍተኛ ሁኔታ ይበልጧቸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት እድሉ ቢሰጣቸው እነዚህን ጄኔራሎች በብቃት መልሰው ሊመሯቸው የሚችሉ መሆኑ ይታወቃል፡፡
የወታደራዊ ሳይንስ ንድፈ ሀሳብ (theory) እንደሚያሳየው አንድ ወታደር መኮንን የሚባለው የአመራር ጥበብ በመውሰድ በተገቢ ሁኔታ ካጠናቀቀ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ ንድፈ ሀሳብ  አንፃር ለህወሓት ጄኔራል መኮንኖች ምን ስም ቢሰጣቸው ይመጥናቸዋል? የበታች ሹም ቢባሉ፣ ለበታች ሹምነት ማዕረግ የሚያበቃውን የአመራር ስልጠና አልወሰዱም፡፡ ከበታች ሹም ቀጥሎ ወደታች ያለው ማዕረግ ቢሰጣቸው ደግሞ እሱንም እንኳን ለማሟላት መደበኛ የሆነውን መሠረታዊ የወታደራዊ  ስልጠናም አልወሰዱም፡፡ በዚህ ነባራቂ ሐቅ በመንተራስ ከተራ ወታደር በስተቀር ሊሰጣቸው የሚችል ምንም ዓይነት መጠሪያ ስም የለም፡፡ ሕወሓቶች ጫካ እያሉም ሆነ አሁን የሚጠራሩበት “ተጋዳላይ እከሌ” “ወዲ እከሌ” የሚለው መጠራሪያቸው የሚመጥናቸው ይመስላል፡፡ ለምሳሌ ሌ/ጄነራል ብለው የሾሙትን ከፍተኛ መኮንን ወዲ ወረዳ እያሉ ይጠራሉ፡፡ ይህ ባጠቃላይ ሲታይ ሠራዊቱ የአንድ መደበኛ ሠራዊት አካልነት ባህሪም ሆነ ተግባር አይታይበትም።
የህወሓት ጄኔራል መኮንኖች የወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ፣ ዕውቀትና አመራር አናሳና ደካማነት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በተጨባጭ በግልጽ የተከሰተበት የታሪክ አጋጣሚ ታይቶ አልፏል:: ይህ ጦርነት እልፍ አዕላፍ የሆኑ የደሃው ኢትዮጵያዊውያን/ት ልጆች ህይወት የተቀጠፈበትና የሀገሪቷ አንጡራ ሀብት የወደመበት አስከፊ ጦርነት ነበር:: ለዚህ ደግሞ ተጠያቂዎቹ:-
1ኛ፡ የሕወሓት ከፍተኛው አመራር እና
2ኛ፡ የህወሐት ስትራቴጂክ አመራር ሰጭ ጄኔራሎች ናቸው
ከላይ የተጠቀሱት የሕወሓት ጄኔራል መኮንኖች  የወታደራዊ ትምህርትና ስልጠና ሳይወስዱ ወይንም ሳይቀስሙ ሠራዊቱን እንዲመሩ በመደረጋቸው ከፍተኛ ጉዳትና አደጋ ደርሷል:: ይህ ሁኔታ ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ ውስጥ መኪና ያለመብራት መንዳት ወይም መኪናን ያለመሪ ለመንዳት እንደሚደረግ ሙከራ ያህል ይቆጠራል::
በአጠቃላይ የመኮንኖች የወታደራዊ አመራር ጥበብ ሥልጠና ምንነትና ይዘት እንዲሁም ሂደቱን እና የመኮንኖች የማዕረግ ዕድገት አሰጣጥ መነሻውም ሆነ መድረሻው የወታደራዊ ትምህርትና ስልጠና መሆኑን በሚገባ ከተጨባጭ ሁኔታ ጋር አይተናል፡፡

2.    ማጠቃለያ

ይህ ጥናታዊ ፅሁፍ በአጠቃላይ የወታደራዊ ትምህርት እና ስልጠና ይዘትና ሂደት ምን እንደሚመስልና  አሁን ያለውን የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚመሩትን ጄኔራል መኮንኖችን  ዓለም ከደረሰበትና  ተቀባይነት ካለው የወታደራዊ ትምህርትና ስልጠና ስታንዳርድ እንፃር የሙያ ብቃት ደረጃቸውን በመመዘንና በመተንተን  በጥልቀት ለመዳሰስ ሙከራ አደርጓል። የወታደራዊ ሳይንስና የአመራር ጥበብ ሥልጠና በተዋረድ ከመሰረታዊ ሥልጠና ወደ ቀጣዩ ስልጠና እንዴት እንደሚሸጋገርና እንደሚገባ፣ ሥልጠናው የሚያካትታቸው የትምህርት ዓይነቶች ፣ ከሥልጠናም በኋላም በኃላፊነት ሊመሩት የሚችሉት ኃይልና የወታደር ብዛት፣ የሥልጠናው የቆይታ ጊዜ፣ እንዲሁም ሥልጠናውን ሲጨርሱ የሚሰጠው የትምህርት ማስረጃ እና ከተወሰነ አገልግሎት በኋላ ከአንዱ የአመራር ሥልጠና ወደ ሌላው የአመራር ሥልጠና እርከን እንዴት እንደሚሸጋገሩ ሥዕላዊ በሆነ መለኩ በማቅረብ ሳይንሳዊ የሆነ የአመራር ሥልጠና ሂደት ዋነኛው እና ትልቁ መንገድ መሆኑን ያመለክታል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ አንድ ጀኔራል መኮንን በሚያዝዘው  ኃይል ውሰጥ ለየእርከኑ አመራር ሰጭ ሊሆኑ  የሚገባቸውን ማዕረጋቸውን፣ የኃላፊነት ቦታና ሠራዊቱ የሚዋጋበትን የጦርነት ህግ፣ ሰራዊቱ የሚሰለጥንበትን የስልጠና ፖሊሲ፣ የወታደራዊ ዶክትሪንና ስትራቴጂ  መቅረጽ መቻል ያለበት መሆኑን ያስረዳል:: አሁን መሬት ላይ ያለው ሐቅ የሚያሳየው ግን ተሿሚዎቹ ክህሎቱ እና ችሎታው የሌላቸው በመሆኑ ከላይ የተዘረዘሩትን አንድ ብቃቱ የተረጋገጠለት ጀኔራል መኮንን ሊፈፅማቸው የሚገባ ተግባራት በብቃት ማከናወን እንደማይችሉ ጥናቱ ያስረዳል:: የእነሱ ዶክትሪንና ስትራቴጂ ቀረጻ መሬት ወረራ ፣ ዝርፊያ፣ ምዝበራ፣ አፈናና ዜጎችን በውጭ ሀገራት ሳይቀር እንዴት መጥለፍ እንደሚቻል ያተኮረ ላቅ ያለ ተንኮል ብቻ ነው:: በአንድ ወቅት ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ጄነራል መኮንኖቹን ሲገመግሙ ያስቀመጡትን ድምዳሜ በመጥቀስ ፅሁፍን እናበቃለን። “እናንተ በቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴም ሆነ በደርግ ዘመነ መንግስት ከነበሩት ጄኔራል መኮንኖች ጋር ስትነፃጸሩ የሰማይና የምድር ያህል ትራራቃላችሁ:: የእናንተ ችሎታ አንድ ሻለቃ  ወይም 400 መቶ ሰው ያለው ሀይል ከማዘዝ  ያለፈ አይደለም!’’
በመጨረሻም ከዚህ በታች በተቀመጠው አባሪ ሰነድ ሰንጠረዥ ፩፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ከ1983 ዓ.ም. አንስቶ እስካሁን ድረስ የጦር ኃይሉ የተዋቀረው በአንድ ብሔር (በትግራይተወላጆች) የበላይነት፣ ያለአንዳች የወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ ሥልጠና መሆኑን ማንም ሊያስተባብለው በማይችል መልኩ ጥሬ ሐቁ ተቀምጧል። ይህ በራሱ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ለምን በዚህ አሳዛኝ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና፣ የማኅበረሰባዊ ዝቅጠት ላይ እንደምትገኝ ቁልጭ አድርገው ከሚያሳዩት ተግዳሮቶች (Factors) አንዱ ሊሆን ይችላል።

3.    አባሪ ሰነድ- ፩ (Annex-1)

 

Amnesty: Sweeping repression in the Oromia region of Ethiopia

Amnesty International
Press releases
28 October 2014
Ethiopia: Ethnic Oromos arrested, tortured and killed by the state in relentless repression of dissent
Thousands of members of Ethiopia’s largest ethnic group, the Oromo, are being ruthlessly targeted by the state based solely on their perceived opposition to the government, said Amnesty International in a new report released today.
“The Ethiopian government’s relentless crackdown on real or imagined dissent among the Oromo is sweeping in its scale and often shocking in its brutality,” said Claire Beston, Amnesty International’s Ethiopia researcher.
“This is apparently intended to warn, control or silence all signs of ‘political disobedience’ in the region.”
More than 200 testimonies gathered by Amnesty International reveal how the Ethiopian government’s general hostility to dissent has led to widespread human rights violations in Oromia, where the authorities anticipate a high level of opposition. Any signs of perceived dissent in the region are sought out and suppressed, frequently pre-emptively and often brutally.
At least 5,000 ethnic Oromos have been arrested between 2011 and 2014 based on their actual or suspected peaceful opposition to the government.
These include peaceful protesters, students, members of opposition political parties and people expressing their Oromo cultural heritage.
In addition to these groups, people from all walks of life – farmers, teachers, medical professionals, civil servants, singers, businesspeople, and countless others – are regularly arrested in Oromia based only on the suspicion that they don’t support the government. Many are accused of ‘inciting’ others against the government.
Family members of suspects have also been targeted by association – based only on the suspicion they shared or ‘inherited’ their relative’s views – or are arrested in place of their wanted relative.
Many of those arrested have been detained without charge for months or even years and subjected to repeated torture. Throughout the region, hundreds of people are detained in unofficial detention in military camps. Many are denied access to lawyers and family members.
Dozens of actual or suspected dissenters have been killed.
The majority of those targeted are accused of supporting the Oromo Liberation Front (OLF) – the armed group in the region.
However, the allegation is frequently unproven as many detainees are never charged or tried. Often it is merely a pretext to silence critical voices and justify repression.
“People are arrested for the most tenuous of reasons: organizing a student cultural group, because their father had previously been suspected of supporting the OLF or because they delivered the baby of the wife of a suspected OLF member. Frequently, it’s because they refused to join the ruling party,” said Claire Beston.
In April and May 2014, events in Oromia received some international attention when security forces fired live ammunition during a series of protests and beat hundreds of peaceful protesters and bystanders. Dozens were killed and thousands were arrested.
“These incidents were far from being unprecedented in Oromia – they were merely the latest and bloodiest in a long pattern of suppression. However, much of the time, the situation in Oromia goes unreported,” said Claire Beston.
Torture
Amnesty International’s report documents regular use of torture against actual or suspected Oromo dissenters in police stations, prisons, military camps and in their own homes.
A teacher told how he had been stabbed in the eye with a bayonet during torture in detention because he refused to teach propaganda about the ruling party to his students.
A young girl said she had hot coals poured on her stomach while she was detained in a military camp because her father was suspected of supporting the OLF.
A student was tied in contorted positions and suspended from the wall by one wrist because a business plan he prepared for a university competition was deemed to be underpinned by political motivations.
Former detainees repeatedly told of methods of torture including beatings, electric shocks, mock execution, burning with heated metal or molten plastic and rape, including gang rape.
Although the majority of former detainees interviewed said they never went to court, many alleged they were tortured to extract a confession.
“We interviewed former detainees with missing fingers, ears and teeth, damaged eyes and scars on every part of their body due to beating, burning and stabbing – all of which they said were the result of torture,” said Claire Beston.
Detainees are subject to miserable conditions, including severe overcrowding, underground cells, being made to sleep on the ground and minimal food. Many are never permitted to leave their cells, except for interrogation and, in some cases, aside from once or twice a day to use the toilet. Some said their hands or legs were bound in chains for months at a time.
As Ethiopia heads towards general elections in 2015, it is likely that the government’s efforts to suppress dissent, including through the use of arbitrary arrest and detention and other violations, will continue unabated and may even increase.
“The Ethiopian government must end the shameful targeting of thousands of Oromos based only on their actual or suspected political opinion. It must cease its use of detention without charge, torture and ill-treatment, incommunicado detention, enforced disappearance and unlawful killings to muzzle actual or suspected dissent,” said Claire Beston.
Interviewees repeatedly told Amnesty International that there was no point trying to complain or seek justice in cases of enforced disappearance, torture, possible killings or other violations. Some were arrested when they did ask about a relative’s fate or whereabouts.
Amnesty International believes there is an urgent need for intervention by regional and international human rights bodies to conduct independent investigations into these allegations of human rights violations in Oromia.
Background
This report is based on more than 240 testimonies collected by Amnesty International, including 176 face-to-face interviews with Oromo refugees collected between July 2013 and July 2014, in four main locations: Nairobi and Kakuma refugee camp, Kenya; Hargeisa, Somaliland; and Kampala, Uganda. Around 40 telephone and email exchanges were conducted with people in different locations in Oromia and in Addis Ababa between 2012 and 2014, and 30 further face-to-face interviews in Ethiopia, Egypt and Kenya between 2011 and 2012. Since 2011, Amnesty International has not been permitted to access Ethiopia to conduct research.

Ginbot 7 held a successful public meeting and fundraising in Oslo on 31 August 2014

This event was part of the worldwide one planned to be held in 26 countries and major cities and held on August 31 starting at 15:00 (3:00 p.m.). This colorful event was organized by the Democratic Change in Ethiopia Support Organization in Norway (DCESON) and Ato Abebe Bogale the deputy chairman of Ginbot 7 was the guest.
DSC_0033
Many Ethiopians living in Oslo and its environs attended the event. The programs of the day began by the participants singing the song of the Ginbot7 popular force and Ato Abi Amare the head of the public relations part of the DCESON, welcomed the participants. A minute of silence was observed for all the victims of the brutal TPLF rule for 23 years.
The first speaker was Ato Debasu Melesu the chairman of the taskforce and conveyed 3 main and strong messages. His first message was to Ato Andargachew Tsige and noted the suffering of the latter in the hands of the TPLF and assured him that the struggle will be intensified and the goal he has been struggling for will be achieved.
DSC_0007
He also stressed that we will make your and our enemies, the TPLF pay for it. His second message was to all who have decided to fight the TPLF and taken up arms and said that we Ethiopians are by your side and you will win. The third message was to the TPLF and he urged them to overcome their inferiority complex and end the imprisonment, persecutions, killings and brutal torture of Ethiopians, Ato Debassu`s speech was followed by the video presentation of the objectives, visions, and missions of Ginbot 7.
The next speaker was Ato Yohannes Alemu chairman of the DCESON and stated that similar events are being or to be held worldwide. He is pleased with the DCESON`s work to organize a similar event in Norway. Moreover, he mentioned about the worsening misrule of the TPLF and its aggravated violations of human rights and repressions in Ethiopia, The only option and solution to these repressions and violations is the removal of the TPLF from power and we all should continue the struggle and participate with concrete actions to attain this goal (removing the TPLF from power).
He pointed out that the time for action has come and we should seize it. In the end he thanked all who contributed to organizing the event. The next speaker was ato Abebe Bogale who was the guest of the day. He mentioned that this event is part of the worldwide one being or to be held in different countries and the messages to be conveyed on are the same (I am also Andargachew Tsige).
He explained the meaning and significance of the rallying motto `I am also Andargachew Tsige` to the participants. Our fellow Ethiopians are fleeing in large numbers to the Arab countries and the rest of the world. The root cause of this flight is the racist and repressive rule of the TPLF and thus it is the responsibility of all Ethiopians to get rid of this dictatorial rule. He also dealt with the reasons for the prolonged rule of the TPLF in Ethiopia.
He went on and said that the TPLF has formed women`s, youth etc. organizations and offers members some benefits to prolong its rule. The young have a special responsibility to remove the TPLF from power. The recent merger agreements among Ginbot 7, patriotic front and Amhara people`s movement will be finalized and the struggle will be stepped up.
The same process will be undertaken with the TPDM and others engaged in the armed struggle. He ended his speech by emphasizing the need to support these mergers and unification.
The fighter Mola the chairman of the TPDM addressed the participants through telephone. He told the participants about the formation of his movement, its present struggle and increasing number of the young from Tigray that are joining it. He said that although the movement bears the name Tigray, it is struggling for the rights of all Ethiopians.
Finally, Ato Daniel Abebe the vice chairman of the DCESON made concluding remarks on Ato Andargachew`s struggle for freedom, democracy, unity and justice. It is time to bring to its end the 23 year brutal, racist, divisive and fascistic rule of the TPLF and urged all to unite and end the rule.
The successful staging of the event was made possible through

የወያኔ ግፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

ዘረኛዉ ወያኔና ባለሟሎቹ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላና በሸኮ መዠንገር አካባቢ የሚያካሄዱትን የማንአለብኝነት የመሬት ዝርፍያና ዜጎችን እርስ በርስ በማጋጨት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያደርጉት አራዊታዊ ሩጫ የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝብ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችል እልቂት እየተፈጸመበት ነዉ። የመዠንገር ህዝብ የሞትና የህይወትን ያክል የማይወጣዉ ምርጫ ስለቀረበለት ተወልዶ ያደገበትን የአባቶቹንና የአያቶቹን አካባቢ ለቅቆ በመዉጣት እራሱን ለመከላከል ባደረገዉ እንቅስቃሴ የብዙ ንጹሃን ዜጎችና ቁጥራቸዉ ቀላል የማይባል ምስኪን ወታደሮችም ህይወት ማለፉ በይፋ እየተሰማ ነዉ። ይህንን ተከትሎ ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች በአካባቢዉ ብዙ ዘመን በቆዩ ብሄሰቦች መካክል ሆን ብለዉ ግጭት እንዲነሳ እያደረጉ በህዝብ መካክል ግጭትትና ዕልቂት የተነሳ በማስመሰል በአካባቢዉ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።
በዚህ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየደረሰ ላለዉ መጠነ ሰፊ ግጭትና ዕልቂት ተጠያቂዉ በአካባቢዉ ለዘመናት አብሮ በመደጋገፍ የኖረዉ ህዝብ ሳይሆን የዚህ አሰቃቂ ዕልቂት ባለቤትና ጠንሳሽ ህወሓትና ዘረኛ መሪዎቹ መሆናቸዉን ለአንድም ደቂቃ ሊዘነጋ አይገባም። ይህ ግጭት ሊነሳ የቻለዉ ህወሓት የአካባቢዉን ደሃ ገበሬ ከትዉልድ መሬቱ ላይ እያፈናቀለ መሬቱን ለከፍተኛ የጦር መኮንኖቹና የኔ ለሚላቸዉ ባለሟሎቹ በማከፋፈሉ መሆኑን ይህንን ግፍ የሚሰማ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ልብ ሊለዉ ይገባል። ህወሃት የአማራን ተወላጆች አካባቢዉ የእናንተ አይደለምና ዉጡ እያለና እያፈናቀለ በሌላ በኩል ግን በየክልሉ የአካባቢዉን ነዋሪ እያፈናቀለ የራሱን ሰዎች የመሬት ባለቤት ማድረጉ አዲስ የጀመረዉ ክስተት ሳይሆን ቆየት ያለና ስር የሰደደ የወያኔ አሰራር ነዉ።
ይህ ዛሬ በጋምቤላና በአካባቢዋ እየደረሰ ያለዉ ግፍና መከራ ለአካባቢዉ ህዝብ ብቻ የሚተዉ ነጠላ ችግር ሳይሆን በአጠቃላይ ወያኔ በአገራችን ላይ ሆን ብሎ በማድረስ ላይ ያለዉ ችግርና መከራ አካል ነዉ። በጋምቤላ ዉስጥ የፈሰሰዉና እየፈሰሰ ያለዉ የሴቶች፤ የወጣቶች፤ የአረጋዉያንና የህጸናት ደም ለሁላችንም የነጻነት ጥሪ እያቀረበልን ነዉ። ይህ የነጻነት ጥሪ ሰምተን የምናልፈዉ ወይም ነገ እንደርሳለን በለን በቀጠሮ የምናልፈዉ ጥሪ አይደለም። ጥያቄዉ የአገርና የዜጎች ህልዉና ጥያቄ ነዉና ነገ ዛሬ ሳንል አሁኑኑ ይህንን የነጸነት ጥሪ ሰምተን ምላሽ ልንሰጠዉ ይገባል።
ይህ ወያኔ በደቡብ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በንጹሃን ዜጎቻችን ህይወት ላይ እየፈጸመ ያለዉ ግፍ በአገራችን ህዝብ ላይ ሲደርስ የመጀመሪያዉ አይደለም፤ ካላቆምነዉ በቀር የመጨረሻዉ እንደማይሆንም አካሄዱ በግልጽ እያሳየን ነዉ። ወያኔ ጋምቤላ ዉስጥ ለምለም መሬት እየፈለገና ነዋሪዉን እያፈናቀለ መሬቱን ለባለሟሎቹ ማደሉን ሳይታቀብ በማንለብኝነት እንደቀጠለበት ነዉ። መሬቱን የተቀማዉ ደሃዉ የጋምቤላ ገበሬም ጫካ እየገባ ከወያኔ ጋር መተናነቁን ቀጥሏል። ትናንት በኦሮሚያ፤ በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል አካባቢዎች በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰዉ ግፍና መከራ ዛሬ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለያዩ ብሄረሰቦች ላይ እየደረሰ ነዉ።
ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ እንቅስቃሴ ይህ ለከቱን የለቀቀ የህወሓት ዕብሪት እንዲተነፍስና በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰዉ ግፍና ሰቆቃ እንዲቆም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ነግ በኔ እያለ የነጻነት ትግሉን እንደቀላቀል የትግል ጥሪ ያደርጋል። ወያኔ እያደረሰ ያለዉ እስራት፤ ድብደባ፤ ግድያና ስደት የሁላችንንም ቤት እያንኳኳ ነዉና ሁላችንም እንደ አንድ ሰዉ ቆመን ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት በትግላችን መደምሰስ አለብን። በጋምቤላና በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የፈሰሰዉ የንጹሃን ወገኖቻችን ደም ደመከልብ ሆኖ የማይቀረዉ ለመብታችንና ለነጻነታችን ቆመን ወያኔን ካስወገድን ብቻ ነዉ።
በህብረት እንነሳ!!!!

Thursday, 23 October 2014

ሃብታሙ አያሌው በጠና ታሟል – ሆስፒታል ነው ዛሬ የዋለው

ሚሊየኖች ድምጽ) የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊና የሚሊዮኖች ግብረ ኃይል ሰብሳቢ የነበሩት፣ አቶ ሃብታሙ አያሌው በጸና መታመማቸዉንና ዛሬ በሆስፒታል መዋላቸዉን ለማረጋገጥ ችለናል።
habtamu ayalew
የማእከላዊ እሥር ቤት ብዙ ቶርቸር የሚደረግበት እስር ቤት እንደሆነ ይታወቃል። አቶ ሃብታሙ አያሌው ከብሎገር አብርሃ ደሳታ፣ ዳን ኤል ሺበሺና የዚዋስ አሰፋ ጋር ሐመሌ 1 ቀን የታሰሩ ሲሆን፣ ፖሊስ «መረጃ ለማሰባሰብ ጊዜ ይሰጠኝ» በሚል አራት ጊዜ ለሃያ ስምንት ፣ ሃያ ስምንት ቀናት መጠየቁ መዘገቡ ይታወሳል። በፍርድ ቤቱ የተቀመጡ ዳኞችም፣ ፖሊሲ ምንም አይነት መረጃ ሳያቀርብ፣ የእነ ሃብታሙን የዋስትና መብት በመከልከልና በወህኒ እንዲቆዩ በመፍቀድ፣ ሕግን የሚያስፈጽሙ ሳይሆን ፣ ለሕጉ ዉጭ በቀጥታ የፖሊስን መመሪያ የሚይሳተናግዱ መሆናቸዉን አሳይተዋል።
አቶ ሃብታሙ በአገራችን ፖለቲክ ትግል በዘመናችን የተነሱ አንጋፋ ፖለቲከኛ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል። ገዢው ፓርቲ በርሳቸው ላይ ኢሰብአዎና ኢፍትሃዊ ግፍ መፈጸሙ በካላላቸው ላይ ጉዳይና ሕመም ቢያስከትለም፣ በመንፈሳቸው ግን ከመቼዉም ጊዜ በላይ ጠንካራ መሆናቸውን ለማወቅ ችለናል።
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/35627#sthash.65J25wuG.dpuf

Wednesday, 22 October 2014

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሕዝብ ወገንተኝነቱን የሚያሳይበት ወቅት አሁን ነው!

ዘረኛውና ፋሽስታዊው የህወሓት አገዛዝ የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት በዘርና በፓለቲካ ወገንተኝነት በመከፋፈል ሹመቱና ጥቅማ ጥቅሙን ለራሱ ወገን፣ ችግሩንና መከራዉን ግን ለሌላው ኢትዮጵያዊ ያደለ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ሳይማሩና ሳይሰለጥኑ የጄኔራልነት ማዕረጎችን በሙሉ ሰብስበው የወሰዱት የህወሓት አባላት መሆናቸው የአደባባይ ሚስጢር ነው።
በወያኔ መዳፍ ውስጥ እየተሰቃየች ባለችው ኢትዮጵያችን ውስጥ በዘርም ይሁን በፓለቲካ አመለካከት ከህወሓት የተለዩ ኢትዮጵያዊያን ቢማሩም ቢሰለጥኑም ለከፍተኛ አመራርነት እንደማይበቁ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ያየነው ነው። አገዛዙ ቅራኔ ውስጥ በገባባቸው ቦታ ሁሉ እየዘመቱ ሕይወታቸውን እየገበሩ ያሉት ግን በመካከለኛና ዝቅተኛ ማዕረጎች ያሉ ኢትዮጵያዊያን መኮንኖችና ብዙሃኑ የሠራዊቱ አባላት የሆኑ ወታደሮችናቸው። ብዙሃኑ የሠራዊት ክፍል አለቆቹን ከመጠበቅ ባለፈ ድምጹን ከፍ አድርጎ ለመናገር እንኳን የማይፈቀድለት ሎሌ ተደርጓል።
ለኢትዮጵያዊ ወታደር ለህወሓት ሎሌ ከመሆን በላይ የሞት ሞት የለም። ብዙሃኑ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊቱ አባላት በጥቂት የወያኔ ሹማምንት የሚረገጥ መሆኑ የሠራዊቱን አባላት የግል ስብዕና ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የሠራዊቱን ክብር ይነካል። የሠራዊታችን የህወሓት አገልጋይ መሆን የምንወዳት አገራችን ኢትዮጵያን ያዋርዳል። ይህ ዉርደት በዚህ ሁኔታ መቀጠል የለበትም።
ከእንግዲህ ጄኔራሎችና ሌሎችም የበላይ አዛዦች ሁሉ የአንድ አካባቢ ተወላጆች በሆኑበት ሠራዊት ውስጥ ተስማምቶ መኖር መቀጠል እያንዳንዱን የመከላከያ ሠራዊት አባል ሊያሰፍር ይገባል። የህወሓት ጄኔራሎች ጮማ በውስኪ ሲያወራርዱ፤ በህንፃዎች ግንባታ፣ በባንኮች ንግድ፣ በግብርናና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ተሰማርተው ቢዝነሳቸውን ሲያጧጥፉ፣ ምስኪኖቹ የሠራዊቱ አባላት በኦጋዴን፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በአማራና በሌሎች የአገሪቱ ግዛቶች እየተወረወሩ ወገኖቻቸውን የሚፈጁበት ሥርዓት ማብቃት አለበት። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ብዙሃኑ አባላት ቤተሰቦቻቸው በችጋር እየተቆሉ የአዛዦቻቸው ሀብት ጠባቂ መሆናቸው ማክተም አለበት።
የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት የጭለማ ዘመን ታሪክ እያበቃ መሆኑን የሚጠቁሙ ምልክቶች እየታዩ ነው። መሣሪያዎቻቸውን እንደያዙ የነፃነት ኃይሎችን የሚቀላቀሉ የሠራዊቱ አባላት ቁጥር ከጊዜ ወደጊዜ እየጨረመ መጥቷል። ሠራዊቱ ከሕዝብ ጎን እንደሚቆም ውስጥ ውስጡን የሚላኩ መልዕክቶች እየተበራከቱ መጥተዋል። ይህ አበረታች ዜና ነው፤ ግን በቂ አይደለም። ወያኔን ከውስጥም ከውጭም የምናጣድፍበት ጊዜው አሁን ነው። የነፃነት ኃይሎችን መቀላቀያ ጊዜ አሁን ነው፤ በሠራዊቱ ውስጥም በህቡዕ መደራጃ ጊዜ አሁን ነው። ይህን ጊዜ መጠቀም ብልህነት ነው።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ጥቂት የህወሓት ጥጋበኞች በብዙሃኑ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ላይ የሚያደርሱት በደል ማብቃት አለበት ይላል። ግንቦት 7፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባላት በሙስና የደለቡት፣ ትዕቢተኛና ጨካኝ መሪዎቻቸው ፍጹም ኢትዮጵያዊ ባህርይ የሌላቸው ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች እንደሆኑ በመረዳት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ክንዱን እንዲያነሳባቸው ጥሪ ያደርጋል። ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሕዝብም የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አንድ ወጥ እንዳልሆነ እና በመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ ያሉ መኮንኖችና አብዛኞዎቹ ወታደሮች የሕዝብ ወገን መሆናቸውን እንዲገነዘብ ያሳስባል። “አብረን ነው ዘረኛውና ፋሽስቱን ወያኔን ከኢትዮጵያ ጫንቃ ላይ አውርደን የምንጥለው” ስንል አብዛኛው የመከላከያ ሠራዊታችን ኢትዮጵያዊ ወገናችን እንደሆነ እና በወደፊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ውስጥም ጉልህ ሚና እንዲጫወት የምንፈልግ መሆኑን ግልጽ ማድረግ እንሻለን። የመከላከያ ሠራዊቱም የሕዝብ ወገንተኝነቱ በተግባር እንዲያሳይ ጥሪ እናደርጋለን። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት የሕዝብ አካል ነው፤ የሕዝብ ወገናዊነቱ በተግባር የሚያሳይበት ትክክለኛ ጊዜ ደግሞ አሁን ነው እንላለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጲያውያን እኔም እንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ በሚል ታላቅ ሕዝባዊ ውይይት አደረጉ

በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጲያውያን እኔም እንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ በሚል ታላቅ ሕዝባዊ ውይይት አደረጉ

OLYMPUS DIGITAL CAMERA
ቅዳሜ ጁለይ 12/2014 በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አዘጋጅነት ሁላችንም እንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን በሚል አላማ በኖርዌ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የደንነት ሀይሎች መታፈንና ለአምባገነኑ የወያኔ መንግስት ታላልፈው መሰጠታቸውን በተመለከተ ወደ ፊት ምን ማድረግ እንዳለባቸው ከተለያዩ ከተሞች በመሰባሰብ በኖርዌ ኦስሎ ለአምስት ሰዓታት የፈጀ ውይይት ሲያደርጉ ውለዋል::
ሕዝባዊ ውይይቱ ከቀኑ 15: 00 ሰአት ላይ የተጀመረ ሲሆን ቁጥራቸው በርከት ያሉ ኢትዮጵያኖች የአቶ እንዳርጋቸው ምስል ያለበትና ሁላችንም እንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን የሚል ጹሁፍ የተጻፉበትን ቲሸርት በመልበስ ለስብሰባው ድምቀት የሰጡት ሲሆን ለአቶ አንዳርጋቸው ያላቸውንም የትግል አጋርነት አስማስክራዋል እነዚህን ቲሸርቶች የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የበርገን ቅርንጫፍ በራሳቸው አነሳሽነት የሰሩ ሲሆን የድጋፍ ድርጅታችን ወጪውን በመሸፈን ለተሰብሳቢው በነጻ ኣድሏል።
ስብሰባውን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት አላፊ አቶ አቢ አማራ በሃያ ሶስት አመታት በወያኔ ጨካኝ አገዛዝ በግፍ ለተገደሉትና በግፍ ለሚሰቃይዩ ወገኖቻችን የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማስደረግ አስጀምረውታል በመቀጠልም አቶ ዮሀንስ አለሙ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ ሊቀመንበር በስብሰባው ላይ የተገኛውን ሕዝብ እንኮን ደህና መጣችሁ በማለትና በማመስገን ፐሮግራሙን በንግግር የከፈቱት ሲሆን አቶ ዮሀንስ በንግግራቸው የወያኔ መንግስት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ባደረሰው አፈና ግንቦት 7 የክተት አዋጅ ማስተላለፉን ጠቅሰው አንባገነኑ የወያኔ መንግስት በአሁን ሰአት በሀገር ቤት በሰላማዊ ትግል እየታገሉ ባሉ ታጋዮች ላይ ሳይቀር እስር እያደረሰባቸው እንዳለ በማመልከት ሰሞንኑን እንኮን የሰመያዊ፣ የአንድነት፣ የአራና የፖለቲካ ድርጅት ከፍተኛ አመራሮች ለስር ተዳርገዋል ብለዋል::
OLYMPUS DIGITAL CAMERAOLYMPUS DIGITAL CAMERA
ስለሆነም ህዝባችንን ለእስር እያደረገ ያለውን አገዛዝ ለመቃወም ሁሉም በአንድነት መሰባሰብ እንዳለበት አጠንክረው በመናገር በአሁን ሰአት የአቶ አንዳርጋቸው በወያኔ መታፈንና መታሰር መላውን ኢትዮጵያ ዳር እስከ ዳር እያንቀሳቀሰውና ሕዝቡም እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ በማለት በስፋት እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ጠቅሰው በአሁን ሰአት ትግሉ የግንቦት 7 ብቻ አይደለም ይህን ትግል በዚሁ አንድ ሆነን መቀጠል እለብን ብለዋል::
በመቀጠል አቶ ደባስ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አባል የአቶ አንዳርጋቸውን ከወጣት እድሜያቸው ጀምሮ ያለውን የፖለቲካ አካሄድ አቶ እንዳርጋቸው ጽጌ ማን ነው ? በሚል ርእስ የአቶ አንዳርጋቸውን የትግል ጉዞ የሚዳስስ ዘገባ ሰፋ ባለ ትንታኔ በጹሁፍ ያቀረቡ ሲሆን በስብሰባው ላይ የኢሀፓ ፣ የአርበኞች ግንባር፣ የሸንጎ ፣የስደተኛው ማህበር ተወካዮች እና ሌሎችም ሰዎች በየተራ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የየድርጅቷቹም ተወካዮች የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በወያኔ መታፈንና ለእስር መዳረግን በተመለከተ የድርጅታቸውን አቋም ለተሰብሳቤው ያስረዱ ሲሆን የሁሉም ፖርቲ ተወካይች በአቶ አንዳርጋቸው መታፈንና ለእስር መደረግ ማዘናቸውን ገልጸው ሁሉም በአንድነት በመተባበር በማንኛውም የትግል እንቅስቃሴ የወያኔንን መንግስት ማስወገድ እንዳለባቸው አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል::
በየፕሮግራሞቹ መሀል ግጥሞችና ሌሏችም ፕሮግራሞች ቀርበው የመጀመሪያው ዞር ተጠናቋል::ከ30 ደቂቃ የእረፍት የሻይ እና የቡና ፕሮግራም በኋላ የሁለተኛው ክፍለ ጊዜ ፕሮግራም በተያዘለት ጊዜ ተጀምሮ የፕሮግራሙን ተሳታፊዎች ያሰተፈ ፕሮግራም በአቶ አብዱ የሱፍ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ስታቫንገር ቅርንጫፍ ምክትል ሊቀመንበር ከግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ልዩ መግለጫና ተግባሪዊ የመጀመሪያ እርከን የትግል ጥሪን ካብራሩ በኋላ ለተሰብሳቢው ለውይይት በማቅረብ በኖርዌ የምንኖር ኢትዮጵያኖች ይህን የትግል ጥሪ ለማስፈጸም ምን እናድርግ በማለት ለውይይት አቅርበው የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች በአቶ ዮሀንስ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌ ሊቀመንበር አወያይ አማካኝነት በስፋት ተወያይተውበታል ::
ተሰብሳቢውም በብዙ ነገሮች ከተወያዩ በኋላ ይሄ ግንቦት 7 ያወጣውን የመጀመሪያ እንከን የትግል ጥሪ ተግባራዊ በየቦታው አለም አቀፍ ታክስ ፎርሶች እየተቋቋሙ እንዳለና በኖርዌይም ይህንኑ ጥሪ ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉንም የፖለቲካ ድርጅቷች ያካተተ ታክስ ፎርስ እንዲቋቋም ተወስኖል:: በመቀጠልም በተሰብሰቢዎች በተመረጡ ሰዎች የተጻፋ ባለ ስድስት አሃዝ የተሰብሳቢው የአቋም መግለጫ ለጉባሄው በጹሁፍ ቀረቦል:: ተሰብሳቢው ያወጣው የአቋም መግለጫ
1. ሁላችንም አንዳርጋቸው ወይም አንድ አርጊያቸው ነን ስንል ለነፃነት፣ ለእኩልነት፣ ለፍትህና ለዲሞክራሲ በሐገራችን ኢትዮጵያ ለማስፈን የሚከፈለውን መስዋእትነት ሁሉ ለመክፈል ዝግጁዎች ነን ማለታችን ነው።
2. የተለያዩ የፖለቲካና ሲቪክ ማህበራት የሚያደርጉትን መጠላለፍ እንዲቀርና በጋራ ወይም አንድ በመሆን እንዲሰሩ ግፊት እናደርጋለን።
3. ለሚቀርብልን ሐገርን የማዳን ጥሪ ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን።
4. የየመን መንግስት ከአለም አቀፍ ህግ ጋራ የሚፃረር ስራ በመስራት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ለወያኔ አሳልፎ በመስጠት የሰራውን ወንጀል ለዓለም አቀፍ ህግ የማቅረብ ስራ በጋራ እንደምንሰራ።
5. የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በወያኔ መታፈን ትግሉን የበለጠ እንደሚያጠናክረውና ወደ ውጤት እንዲያመራ የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናደርጋለን።
6. ወያኔ የተለያየ ምክንያት በመፍጠር ኢትዮጵያውያንን እስርቤት ማስገባቱን እንዲቀርና የታሰሩትን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ እንጠይቃለን በማለት የአቋም መግለጫ አውጥተዋል ።
በመጨረሻም አቶ ዳንሄል አበበ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ምክትል ሰብሳቢ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የአቋም መግለጫ ለተሰብሳቢው በጹሁፍ ያሰሙ ሲሆን በንግግራቸውም አቶ እንዳርጋቸው ጽጌ ለኢትዮጵያ አንድነትና ነጻነት የቋሙ የነጻነት ታጋይ ናቸው እኔም እንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ የምንል ሁሉ ለሃያ ሶስት አመታት ህዝብን በዘረኝነት የከፋፈለውን ወያኔን በቃ ልንለው ይገባል ካሉ በኋላ በኢትዮጵያ ከመቸውም ጊዜ በላይ አፈና፣ ግድያው፣ እስራቱ መጨመሩን በመናገር ይኼን ጨቋኝና አፋኝ ስርአት ለማስወገድ እንነሳ በማለት ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን በመጨረሻ እኔ እንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ እናንተስ በማለት የፕሮግራሙን ተሳታፊ በመጠየቅ ፕሮግራሙ በተያዘለት ሰዓት ከምሽቱ 20:00 ተጠናቋል ::
እኛ ሁላችንም እንዳርጋቸው ጽጌዎች ነን!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!
በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ